Fana: At a Speed of Life!

የሐዋሳ እና አዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች 50 ሚሊየን የአፍና አፍንጫ መሸፈኛዎችን በማምረት ለትምህርት ሚኒስቴር ማቅረብ ጀመሩ

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 4 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የሐዋሳ እና አዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች 50 ሚሊየን የአፍና አፍንጫ መሸፈኛዎችን በማምረት ለትምህርት ሚኒስቴር ማቅረብ ጀመሩ
40 ሚሊየን የአፍና አፍንጫ መሸፈኛዎች ከሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ እንዲሁም 10 ሚሊየን ደግሞ ከአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ለትምህርት ሚኒስቴር የሚቀርቡ ሲሆን የመጀመሪያው 5 ሚሊየን ጭምብልም ርክክብ ተከናውኗል፡፡
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርከ በመገኘት የመጀመሪያውን ዙር የአፍና አፍንጫ መሸፈኛዎች መረከባቸውን ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.