Fana: At a Speed of Life!

በቻምፒየንስ ሊጉ ባርሴሎና ጁቬንቱስን ከሜዳው ውጭ አሸንፎታል

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 18 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታዎች ምሽቱን ተካሄደዋል።

ከምድብ አምስት እስከ ስምንት ባሉት ቡድኖች መካከል በተካሄደ ጨዋታ ታላላቆቹ ቡድኖች ድል ቀንቷቸዋል።

በምድብ አምስት የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ከሜዳው ውጭ ክራስኖዳርን 4 ለ 0 እንዲሁም ሲቪያ ሬኔስን 1 ለ 0 አሸንፈዋል።

በምድብ ስድስት ቦሩሲያ ዶርትመንድን ዜኒትን 2 ለ 0 ሲያሸንፍ ክለብ ብሩጅ ከላዚዮ ያደረጉት ጨዋታ ደግሞ አንድ አቻ ተጠናቋል።

ተጠባቂው ጨዋታ በምድብ ሰባት ጁቬንቱስን ከባርሴሎና አገናኝቷል።

ጨዋታውን ባርሴሎና 2 ለ 0 ሲያሸንፍ ደምበሌ እና ሜሲ የድል ጎሎቹን አስቆጥረዋል።

የሃንጋሪው ኤፍ ቲ ሲ ከዳይናሞ ኬቭ ያደረጉት ጨዋታ ደግሞ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት ፍጸሜውን አግኝቷል።

በምድብ ስምንት ደግሞ ማንቼስተር ዩናይትድ አር ፒ ሌፕዚግን 5 ለ 0 በሆነ ሰፊ የጎል ልዩነት መርታት ችሏል።

በምድቡ ሌላኛ ጨዋታ ከሜዳው ውጭ የተጫወተው ፒ ኤስ ጂ ኢስታንቡል ባሻክሼርን 2 ለ 0 አሸንፎ ተመልሷል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.