Fana: At a Speed of Life!

የምዕራብ ጎጃም ዞን ነዋሪዎች ከ290 በላይ ሰንጋና ፍየል ለሀገር መከላከያ ሰራዊትና ለአማራ ልዩ ሀይል ድጋፍ አደረጉ

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 3 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የምዕራብ ጎጃም ዞን ነዋሪዎች ከ290 በላይ ሰንጋና ፍየል ለሀገር መከላከያ ሰራዊትና ለአማራ ልዩ ሀይል ድጋፍ አደረጉ፡፡

የምዕራብ ጎጃም ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ሀላፊ አቶ አንማው ዳኛቸው÷ ከዞኑ ስምንት ወረዳ ነዋሪዎች ከ6 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን ገልፀዋል፡፡

ከዚህ ውስጥም በ3 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር 134 ሰንጋ፣ 156 ፍየልና 10 በጎችን በመግዛት እንዲሁም 3 መኪና ደረቅ ምግብ ድጋፍ መደረጉን ተናግረዋል፡፡

ድጋፉን ማዕከላዊ ጎንደር የሚገኘው የሎጀስቲክ ስምሪት ይረከባልም ነው ያሉት አቶ አንማው፡፡

ዞኑ ከዚህ በፊትም መሰል ድጋፍ ማድረጉንም አስታውሰዋል፡፡

 

በናትናኤል ጥጋቡ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.