Fana: At a Speed of Life!

ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ከሳዑዲ ዓረቢያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 20 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ከሳዑዲ ዓረቢያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፈይሰል ቢን ፋርሃን ቢን አብዱላህ ጋር ተወያዩ።

በውይይታቸውም በሁለቱ ሃገራት የሁለትዮሽ ግንኙነትና በጋራ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።

ዶክተር ሙላቱ ተሾመ በትናንትናው እለት ነበር ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ ያቀኑት።

ሪያድ ንጉስ ካሊድ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም በሳዑዲ አረቢያ የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር ፕሮፌሰር አህመድ ቢን አብዱላዚዝ ቃታን አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ምንጭ፦ spa.gov.sa

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.