በሀረሪ ክልል ለመከላከያ የሚደረገውን ድጋፍ በማስመልከት ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት እየተደረገ ነው
አዲስ አበባ፣ ህዳር 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሀረሪ ክልላዊ መንግስት “ሁሉን አቀፍ ድጋፍ ለመከላከያ ሰራዊታችን!” በሚል መሪ ቃል ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት እየተደረገ ነው።
በህዝባዊ የውይይት መድረኩ ላይ ወቅታዊ የሀገራዊ ሁኔታን በሚመለከት ውይይት እንደሚደረግ የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል፡፡
በውይይት መድረኩም የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ፣ምክትል ርዕሰ መስተዳድር
ሚስራ አብደላ፣ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ አዲስአለም በዛብህን ጨምሮ የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባገዳዎች፣ የሀይማኖት አባቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።
ሚስራ አብደላ፣ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ አዲስአለም በዛብህን ጨምሮ የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባገዳዎች፣ የሀይማኖት አባቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።