Fana: At a Speed of Life!

የኢጋድ ዋና ጸሃፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በሱዳን ጉብኝት እያደረጉ ነው

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 30፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) ዋና ጸሃፊ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ በሱዳን ጉብኝት እያደረጉ ነው።

በሱዳን ቆይታቸው በትናንትናው እለት የወቅቱ የኢጋድ ሊቀመንበር እና የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ ጋር ተወያይተዋል።

በውይይታቸውም በኢጋድ የማሻሻያ ስራዎች ዙሪያ መወያየታቸውን በፌስቡክ ገፃቸው አስታውቀዋል።

የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ በበኩላቸው፥ ሀገራቸው ለኢጋድ የማሻሻያ ስራዎች የበኩሏን እንደምትወጣ እና ሌሎች አባል ሀገራትም ተመሳሳይ ስራ እንዲሰሩ እንደምትጠይቅ ገልፀዋል።

አብደላ ሀምዶክ በቅርቡ ወደ ጅቡቲ በማቅናት የኢጋድን ዋና ጽህፈት ቤት እንደሚጎበኙ እና ለአዲሱ ጽህፈት ቤት ህንፃ ግንባታ መሰረት እንደሚያስቀምጡም ዶክተር ወርቅነህ ጠቅሰዋል።

ዶክተር ወርቅነህ በዛሬው እለት ከሱዳኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አስማ አብደላ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።

በውይይታቸውም የኢጋድን አቅም ማሳደግ በሚቻልበት አግባብ፣ በኢጋድ የማሻሻያ ስራዎች እና በሌሎች ጉዳዮች ላይ መክረዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.