Fana: At a Speed of Life!

በቻምፒየንስ ሊጉ ሪያል ማድሪድ እና ማንቼስተር ሲቲ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 8፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ትናንት ምሽት ሁለት ጨዋታዎች ተካሄደዋል፡፡

ማንቼስተር ሲቲ ቦሩሲያ ሞንቼግላድባህን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ባሸነፈበት ጨዋታ፥ ኬቪን ደብሩይነ እና ኢካይ ጉንዶኻን የድል ጎሎቹን አስቆጥረዋል፡፡

በደርሶ መልስ ውጤት ማንቼስተር ሲቲ 4 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል፡፡

በሌላ ጨዋታ ሪያል ማድሪድ አታላንታን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

ካሪም ቤንዜማ፣ ሰርጂዮ ራሞስ እና ማርኮ አሴንሲዮ የማሸናፊያ ጎሎቹን ለሪያል ማድሪድ ሲያስቆጥሩ፥ ሙሪዬል ደግሞ ለአታላንታ የማስተዛዘኛ ጎሏን ማስቆጠር ችሏል፡፡

ውጤቱን ተከትሎ ሪያል ማድሪድ በደርሶ መልስ ውጤት 4 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የሩብ ፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን አረጋግጧል፡፡

ፒ ኤስ ጂ፣ ቦሩሲያ ዶርትመንድ፣ ሊቨርፑል እና ፖርቶ ቀደም ብለው ሩብ ፍጻሜውን መቀላቀላቸው ይታወሳል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.