በኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል የተመራ ልዑክ ለስራ ጉብኝት ደቡብ ሱዳን ገባ
አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 11 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል እና ልዑካናቸው ለስራ ጉብኝት ደቡብ ሱዳን ጁባ ገብቷል ።
የልዑካን ቡድኑ ጁባ የገባው በደቡብ ሱዳኑ ብሔራዊ ፖሊስ አገልግሎት ሃላፊ ጄኔራል ማጃክ አከክ ግብዣ መሆኑ ተመላክቷል።
ሁለት የፖሊስ አዛዦች በሁለቱ አገራት ትብብር ዙሪያ እንደሚወያዩ ተገልጿል ፡፡
በዚህም በድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ፣ በሁለቱም አገራት የፖሊስ መኮንኖች የመረጃ ልውውጥ እና ስልጠና መስኮች እንደሚወያዩ ከደቡብ ሱዳን ብሔራዊ ፖሊስ አገልግሎት ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!