Fana: At a Speed of Life!

በወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ የተመራ ልዑክ በሻሸመኔ ከተማ እየተገነቡ የሚገኙ መሰረተ ልማቶችን ጎበኘ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 17፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና በከተማ ልማት አስተባባሪ ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ የተመራ የልዑካን ቡድን በሻሸመኔ ከተማ እየተገነቡ የሚገኙ መሰረተ ልማቶችን ጎበኘ፡፡
በጉብኝቱ ከወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ በተጨማሪ የኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ የአደረጃጀት እና ፖለቲካ ሃላፊ አቶ ሳዳት ናሻን ጨምሮ የተለያዩ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
ቡድኑ በከተማው በ38 ሚሊየን ብር እየተገባ የሚገኘውን የመጠጥ ውሃ ግንባታ ፕሮጀክትንም ጎብኝቷል፡፡
በሻሸመኔ ከተማ ከዚህ በፊት በሶስት ፓምፖች ሲሰጥ የነበረው የንጹህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት ወደ 10 ፓምፖች ማደጉ ተገልጿል፡፡
በከተማው የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋኑ 45 በመቶ የነበረው ወደ 60 በመቶ ማደጉም ነው የተገለጸው፡፡
በጉብኝቱ ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ በማንኛውም አገልግሎት የህብረተሰቡን ፍላጎት ለማርካት በሃላፊነት እና በታማኝነት መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በጂብሪል ሃሰን
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.