Fana: At a Speed of Life!

የጤና ሚኒስቴር የብቃት ምዘና ፈተና መስጠት ጀመረ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 20 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስቴር የብቃት ምዘና ፈተና መስጠት መጀመሩን አስታወቀ፡፡

ፈተናው በህክምና፣ ነርሲግ፣ ጤና መኮንን፣ አኒስቴዥያ ፣ ሜዲካል ላቦራቶሪ ቴክኖሎጅ፣ ፋርማሲ እና ሚድዋይፈሪ ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ለተመረቁ ባለሙያዎች ከዛሬ ጀምሮ እስከ መጋቢት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ የብቃት ምዘና ፈተና መስጠት ጀምሯል፡፡

ፈተናው በመላ ሀገሪቱ በተዘጋጀ 38 የፈተና መስጫ ጣቢያዎች የሚሰጥ ሲሆን የፈተና አሰጣጥ ስርአቱን የጤና ሚኒስትር ዲኤታ ወይዘሮ አለምፀሀይ ጳውሎስ እና የሀገር አቀፋ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዲላሞ ኦቶሬ ከመፈተኛ ጣቢያዎች አንዱ በሆነው የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ በመገኘት ጎብኝተዋል፡፡

የብቃት ምዘና ፈተና የሚወስዱ 18 ሺህ 926 ተመዛኞች ሲሆኑ ጤና ባለሙያዎች አገልግሎት መስጠት ከመጀመራቸው በፊት ብቃታቸውንና ክሎታቸውን ለመመዘን የሚሰጥ ፈተና ነው፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.