Fana: At a Speed of Life!

ባለፉት ሰባት ቀናት 14 ሺህ 437 ግለሰቦች በኮቪድ19 ተይዘዋል

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 24 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት ሰባት ቀናት ከመጋቢት 17 እስከ መጋቢት 23 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ 14 ሺህ 437 ግለሰቦች በኮቪድ19 መያዛቸው የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት አስታወቀ፡፡

የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 100 ግለሰቦች ውስጥ 25ቱ ቫይረሱ እንደተገኘባቸውም ኢንስቲቲዩቱ ገልጿል፡፡

በዚህ ጊዜ ውስጥም 149 ግለሰቦች ህይወታቸውን አጥተዋልም ነው ያለው፡፡

በትናንትናው እለት ለ8 ሺህ 294 ግለሰቦች የላቦራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን፥ 2 ሺህ 372 ሰዎች ኮቪድ-19 ሲገኝባቸው ይህም ከ100 ሰዎች 29ኙ ላይ ቫይረሱ እንደተገኘ ያሳያል ነው ያለው፡፡

አሁን ላይም የቫይረሱ ስርጭት በመላ ሃገሪቱ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩንም ነው ኢንስቲቲዩቱ የገለጸው፡፡

ከዚህ ጋር ተያይዞም ህብረተሰቡም ሆነ መንግስታዊ አካላት የወጡ መመሪያዎችን በመተግበርና በሃላፊነት ስሜት በመንቀሳቀስ የቫይረሱን ስርጭት እንዲከላከሉም ጥሪ አቅርቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.