በልዩ ልዩ ኃላፊነትና በመንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ የበላይ ጠባቂነት ያገለገሉት ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ አረፉ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 28፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በልዩልዩ ኃላፊነትና በመንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ የበላይ ጠባቂነት ያገለገሉት ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) አረፉ፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ እና የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የበላይ ጠባቂ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ዛሬ ተገልጿል፡፡
ከአባታቸው ባራምባራስ ተስፋ ተክሉ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ታህሣ ኃይሉ በ1930 ዓ.ም ግንቦት ወር በትግራይ ክልል ብዘት ወረዳ የተወለዱት ብፁዕነታቸው÷ በተወለዱ በ83 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን የቅዱስ ሲኖዶስ ጽህፈት ቤት መግለጹን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅትን ጠቅሶ ኢዜአ ዘግቧል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!