Fana: At a Speed of Life!

ድሬዳዋ ለመቄዶንያ 100 ሺህ ካሬ ሜትር የመሬት ካርታ አስረከበች

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 3፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል 100 ሺህ ካሬ ሜትር የመሬት ካርታ አስረከበ።

አረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማንን ከጎዳና በመሰብሰብ የላቀ ሰብዓዊነት ያለው መቄዶንያ ‹‹ሰው ለመርዳት ሰው ብቻ መሆን በቂ ነው›› የሚል መርህ አንግቦ ዓመታትን አስቆጥሯል።

በእነዚህ ዓመታትም በርካታ አረጋውያንንና የአዕምሮ ሕሙማንን ከጎዳና ሕይወት መታደግ የቻለ የበጎ አድራጎት ተቋም መሆኑ ይታወቃል።

ማዕከሉ በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች ወገኖችን ከጎዳና በማንሳትና የተረጂዎችን ቁጥር በሦስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ወደ 10 ሺህ ለማድረስ እየሰራም ይገኛል።

ምንጭ፡-ኢዜአ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.