Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ሣህለ-ወርቅ ከተመድ የስነ-ሕዝብ  ፈንድ የኢትዮጵያ ተወካይ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ፕሬዚዳንት ሣህለ-ወርቅ ዘውዴ አዲሷን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስነ-ሕዝብ ፈንድ የኢትዮጵያ ተወካይ ጋር ተወያዩ፡፡

ተወካይዋ በሀገሪቱ ውስጥ የተጀመሩትን ማሻሻያዎች ለመደገፍ የተመድ የስነ-ሕዝብ ፈንድን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል፡፡

ሴቶችን ያካተተ እድገት ማስመዝገብ በሚቻልበት መንገድ ላይ ድርጅታቸው በተለይ ጠንክሮ እንደሚሰራ ተወካይዋ ገልጸዋል::

ፕሬዚዳንት ሣህለ-ወርቅ የተባበሩት መንግስታት የኢትዮጵያ ብሄራዊ የልማት ግቦች እንዲሳኩ በማድረግ ላይ ያለውን ጥረት ማድነቃቸውን ከፕሬዚዳንት ጽህፍት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.