የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የመራጮች ምዝገባ ለሚቀጥሉት 15 ቀናት በኢንተርኔት ሊካሄድ ነው
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 12፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የመራጮች ምዝገባ ለሚቀጥሉት 15 ቀናት በኢንተርኔት መመዝገብ እንደሚችሉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ፡፡
ቦርድ ተማሪዎቹ እስከሚያዝያ 26 ድረስ በቦርዱ ድረገጽ እና በማህበራዊ ገጾች በሚገኘው ማስፈንጠሪያ ወይንም ሊንክ በመጠቀም መመዝገብ እንደሚችሉ ነው የገለጸው፡፡
ቦርዱ የፓለቲካ ፓርቲዎች፣ መገናኛ ብዙኀንና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ይህንን የኦንላየን ምዝገባ ለተማሪዎች በማስተዋወቅ እንዲተባበሩ ጥሪ አቅርቧል፡፡
የመመዝገቢያ ሊንክ – http://www.nebe.org.et/ovrs
ኦንላይን የመራጮች ምዝገባ ስርዓት መምሪያ
https://drive.google.com/file/d/1ZH3rlNvGKgiRGbf6goB_09dZ_XC5k3ZL/view?fbclid=IwAR0AxyNgUu-eqDzbYDaq_6wJ1cn-d5O_0h6_0gbpwliCaADXZtWpR1afptk
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!