Fana: At a Speed of Life!

በጅግጅጋ ከተማ በ60 ሚሊየን ብር ለሚገነባው ቤተ መጽሐፍት የመሰረት ድንጋይ ተጣለ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 18 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በጅግጅጋ ከተማ በ60 ሚሊየን ብር ለሚገነባው የህዝብ ቤተ መጽሐፍት የመሰረት ድንጋይ ተጣለ፡፡

የመሰረት ድንጋዩ የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ዑመርን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ነው የተጣለው፡፡

ለቤተ መጽሐፍቱ የሚወጣው ወጪ ሙሉ በሙሉ በክልሉ መንግስትና ከህዝብ በሚሰበሰብ ገንዘብ እንደሚሸፈን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በፌስ ቡክ ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡

ቤተ መጽሐፍቱ በምስራቅ አፍሪካም በአይነቱ የመጀመሪያ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.