Fana: At a Speed of Life!

አዲሱ የፌደራል ኢንተርፕራይዝ ልማት ስትራቴጂ  ስራ አጥነትን  ለመቀነስ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተገለጸ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 19 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)  አዲሱ የፌደራል ኢንተርፕራይዝ ልማት ስትራቴጂ ዘላቂና አመርቂ ስራዎችን በመፍጠር የስራ አጥነት ምጣኔን በመቀነስ ረገድ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተገለጸ።

ስትራቴጂው በፌደራል ስራ እድል ፈጠራ ኮሚሽን አማካኝነት የተዘጋጀ ነው::

ኮሚሽኑ የፌደራል ኢንተርፕራይዝ ልማት ስትራቴጂው ላይ ከከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት እያካሄደ ነው::

በውይይቱ ላይ ኮሚሽነሩ አቶ ንጉሡ ጥላሁን ጨምሮ የዘርፉ ባለድርሻ አካላትና ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል::

ስትራቴጂው ከአገልግሎት አሰጣጥ ጀምሮ ያሉ ሌሎች አስተዳደራዊ አሰራሮችን የሚፈትሽና የሚያሻሽል ነው ተብሏል ::

ስትራቴጂው ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ የተዘጋጀ ሲሆን ÷ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ ያለውን ነባር ስትራቴጂ በጉልህ የሚያሻሽልና የሚቀይር መሆኑም  ተገልጿል::

በዋናነትም እስካሁን ማነቆ ሆነው ዘርፉ እንዳያድግ ሲያደርጉ የቆዩ ችግሮች መለየታቸውንና  መሻሻላቸውም በውይይቱ ላይ ተነስቷል::

ስትራቴጂው ተግባራዊ ከተደረገ በሚቀጥለው 10 አመት ውስጥ ለ20 ሚሊየን ዜጎች የስራ ዕድል እንደሚፈጥር ተመላክቷል።

የውይይቱ ተሳታፊዎችም ስትራቴጂው ላይ ሊካተቱ የሚገባቸውና ትኩረት ሊስጥባቸው የሚገቡ ሀሳቦችን እያነሱ ይገኛሉ::

በዘቢብ ተክላይ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.