ጠ/ሚ ዐቢይ የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋሩ
አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 24፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋሩ ።
በአንድነት ፓርክ በተካሄደው የማዕድ ማጋራት ላይ አረጋውያን ፣ አርበኞች ፣ አካል ጉዳተኞችና ችግረኛ ታዳጊዎች ታድመዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩና ቤተሰባቸው በዓሉን በታላቁ ቤተ መንግሥት አንድነት ፓርክ ውስጥ ከ210 ዜጎች ጋር አሳልፈዋል።
በአላዛር ታደለ