Fana: At a Speed of Life!

ከቁጥጥር ውጪ የሆነው የቻይና ሮኬት በህንድ ውቂያኖስ ላይ አረፈ

 

አዲስ አበባ ፣ግንቦት 1፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) “ከቁጥጥር ውጭ ሆኗል” የተባለው የቻይናው ሮኬት በህንድ ውቅኖስ ላይ ማረፉ መረጋገጡን የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ኢንስትቲዩት አስታወቀ።

የኢንስትቲዩቱ ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ ለኢቲቪ እንደገለፁት የቻይና ሎንግ ማርች 5ቢ ሮኬት ተወሰነ ክፍሉ መሬት ላይ ሳይደርስ የተቃጠለ ሲሆን የቀረው ስብርባሪም በህንድ ውያኖስ ማልዲስ ደሴት አቅራቢያውቅያኖስ ውስጥ አርፏል።

5 ቢ ሮኬት ከቁጥጥር ውጭ ከሆነበት ከሚያዝያ 21 ቀን 2013 ዓ.ም. እንስቶ በከፍተኛ ፍጥነት በመሬት ዙሪያ ሲሽከረከ መቆየቱ ይታወሳል።

ኢንስትቲዩቱ ከዚህ በፊት ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንዳስታወቀው በመሬት ዙሪያ ለመዞር የሚፈጅበት ጊዜ 90 ደቂቃ ሲሆን ፍጥነቱም በስዓት 28 ሺህ ኪ.ሜ ይደርሳል ነው ያለው።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡-https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.