Fana: At a Speed of Life!

ሜጋ ፕሮጀክቶችን በተለያየ የቢዝነስ መስክ የተሰማሩና ተጽዕኖ ፈጣሪ  ግለሰቦች ጎበኙ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 1 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚገኙ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በተለያየ የቢዝነስ መስክ የተሰማሩናተጽዕኖ ፈጣሪ  ግለሰቦች ጎብኝተዋል፡፡

በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ  ሴክታሪያት አማካይነት በተዘጋጀው በዚህ ጉብኝት 40 ከተለያየ ኩባንያዎች የተውጣጡ ስራ ፈጣሪዎች እና ባለቤቶች ተገኝተዋል ።

በጉብኝቱም አጠቃላይ የፕሮጀክቶቹ ፋይዳ፣ የግንባታ ሂደት ፣ የሚፈጥሯቸው ሀገራዊ አቅሞች እና ተያይዘው የሚፈጠሩ እድሎች ተገልጸዋል ።

ጎብኚዎቹ በተለያየ የቢዝነስ መስክ የተሰማሩ በመሆናቸው ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድ ሚናቸውን እንዲወጡ ጉብኝቱ  ያግዛቸዋል ተብሏል ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት እድሳት ፣ የአድዋ ዜሮ ዜሮ ፕሮጀክት ፣ ከመስቀል አደባባይ ማዘጋጃ ቤት የማስዋብ ስራ ፣ የመስቀል አደባባይ ፕሮጀክት እንዲሁም የቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት ማስፋፊያን ጎብኚዎቹ ተመልክተዋል ።

በዓልአዛር ታደለ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.