Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያና ኩባ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ በትብብር የመስራት ፍላጎታቸውን ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያና ኩባ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ በትብብር ለመስራት ያላቸውን ፍላጎት ገልጸዋል፡፡

በኩባ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሽብሩ ማሞ ከኩባ የሳይንስ ቴክኖሎጂና የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትር ኤልባ ሮዛ ፔሬዝ ሞንቶያ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸው ወቅትም ሃገራቱ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ የተፈረሙ የመግባቢያ ስምምነቶችን መተግበር በሚቻልበት አግባብ ላይ መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

ሃገራቱ በባዮቴክኖሎጂ፣ ሜትሮሎጂ እና ሥነ ፈለክ ጨምሮ በሳይንስና ቴክኖሎጂ በትብብር መስራት በሚቻልበት አግባብ ላይም መክረዋል፡፡

አምባሳደር ሽብሩ ስለመጪው ምርጫ፣ የታላቁ ህዳሴ ግድብ፣ ስለኢትዮ-ሱዳን የድንበር ውዝግብ እና በትግራይ ክልል እየተከናወነ ስላለው የሰብዓዊ ዕርዳታ እና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ለሚኒስትሯ ገለጻ አድርገውላቸዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.