Fana: At a Speed of Life!

በ205 ሚሊየን ብር ለሚገነባው የታርጫ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 14 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እርስቱ ይርዳ በዳውሮ ዞን በ205 ሚሊየን ብር ለሚገነባው የታርጫ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የመሠረት ድንጋይ አኖሩ።

የከተማው ነዋሪ የታርጫ ከተማ የንጹህ መጠጥ ውሃ ችግር አሳሳቢ እንደነበር ከዚህ ቀደም ለምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ጥያቄ አቅርቦላቸው ነበር።

ነዋሪዎቹ የህዝቡን የንጹህ መጠጥ ውሃ ጥያቄ መነሻ በማድረግ የክልሉ መንግስት ለሰጠው ፈጣን ምላሽ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዞኑ ከህዝብ ተወካዮች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ከደቡብ ክልል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.