Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ በ1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር የተገነቡ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተመረቁ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ በ1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር የተገነቡ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ተመርቀዋል።

በ2013 ዓ.ም የከተማ አስተዳደሩ 1 ሺህ ፕሮጀክቶችን ማጠናቀቅ መቻሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በምረቃው ላይ ተናግረዋል።

በጥቅሉ በቀን 90 ሺህ ሜትር ኪዩብ ውሃ መስጠት የሚያስችሉ የከርሰ ምድር የጥልቅ ጉድጓድ የንፁህ ውሃ ፕሮጀክቶች የተመረቁ ሲሆን፥ ከእነዚህ መካከል የቱሎ ጉዶ ፕሮጀክት በቀን 68 ሺህ ሜትር ኪዩብ ውሃ መስጠት የሚችል ነው ተብሏል።

ፕሮጀክቱ አቃቂ ቃሊቲ፣ ቦሌ፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ እና ቂርቆስ ክፍለ ከተሞች እንዲሁም ፕሮጀክቱ በተገነባበት አካባቢ ለሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የንፁህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት እንደሚሰጥ ኢቢሲ ዘግቧል።

ከዚህ ጎን ለጎን የከፋ የውሃ ችግር ባለባቸው በተለያዩ አካባቢዎች ከተገነቡ ጉድጓዶች መካከል በቀን 22 ሺህ ሜትር ኪዩብ መስጠት የሚችሉ የውሃ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት በቅተዋል።

ለፕሮጀክቶቹ ከ1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገባቸው ተገልጿል።

ፕሮጀክቶቹ የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ውሃ የማምረት አቅምን ከ574 ሺህ ወደ 664 ሺህ ሜትር ኪዩብ ማሳደጋቸው ተነግሯል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.