Fana: At a Speed of Life!

ሴናተር ጂም ኢንሆፍ በኢትዮጵያ የስራ ሃላፊዎች ላይ የተጣለውን የቪዛ ክልከላ ተቃወሙ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 18 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካዋ ኦክላሆማ ግዛት ሴናተር ጂም ኢንሆፍ ዋሽንግተን በኢትዮጵያ የስራ ሃላፊዎች ላይ የጣለችውን የቪዛ ክልከላ ተቃወሙ፡፡

ሴናተሩ ኢትዮጵያ የአሜሪካ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋት በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ አስታውቀዋል፡፡

ኢትዮጵያ አሁን ላይ የሽብር ቡድኖችን እንቅስቃሴ ለመግታት እየሰራች መሆኑን ገልጸዋል፡፡

መሰል እርምጃዎችም ሰላማዊ ውሳኔዎች ላይ ለመድረስ የሚደረገውን ጥረት የማያግዙ ናቸውም ብለዋል፡፡

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር በኢትዮጵያ የስራ ሃላፊዎች ላይ የቪዛ ክልከላ የሚጥል ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.