Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮ ቴሌኮም በማዕከላዊ ምስራቅ ሪጅን የ4ጂ ኤል ቲ አድቫንስ የሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት አስጀመረ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 19፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮ ቴሌኮም በማዕከላዊ ምስራቅ ሪጅን በሐረር፣ አወዳይና ሀረማያ ከተሞች የ4ጂ ኤል ቲ አድቫንስ የሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት አስጀመረ።

ኢትዮ-ቴሌኮም በማዕከላዊ ምስራቅ ሪጅን ያስጀመረው የ4ጂ ኤል ቲ አድቫንስድ የሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት 67 ሺህ ደንበኞችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑም ተገልጿል።

የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ በማዕከላዊ ምስራቅ ሪጅን በሐረር፣ አወዳይና ሀረማያ ከተሞች ፈጣን የሞባይል ኢንተርኔት መጠቀም የሚያስችለውን የ4ጂ ኤል ቲ አድቫንስድ አገልግሎት አስጀምረዋል።

አገልግሎቱ በሪጅኑ የነበረውን የኢንተርኔት ፍጥነት በ14 እጥፍ እንደሚያሻሽለውም  መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

የኢትዮ-ቴሌኮም በምስራቅ ሪጅን በድሬዳዋ፣ ጭሮና አይሻ ከተሞች የ4ጂ ኤል ቲኢ አድቫንስድ የሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት በያዝነው ሳምንት ማስጀመሩ የሚታወስ ነው።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.