Fana: At a Speed of Life!

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የስራ አፈጻጸም የሚገመግም የውይይት መድረክ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የስድስት ወራት ስራ አፈጻጸምና ቀጣይ አቅጣጫዎችን የሚገመግም የውይይት መድረከ በመቀሌ ከተማ ተጀመረ።

መድረኩ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ሲጀመር የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር አብረሃም በላይ እንደገለጹት፥ በመድረኩ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ባለፉት ስድስት ወራት የተከናወኑ ስራዎች ይገመገማሉ።

በተለይም በክልሉ የጸጥታ ሁኔታ፣ ለተፈናቀሉ ወገኖች የሰብአዊ እርዳታ አሰጣጥ እና የኮሮና ቫይረስ መከላከል ላይ ስለተከናወኑት ተግባራት ውይይት እንደሚደረግባቸው አስታውቀዋል።

እንዲሁም በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ስራ አፈጻጸምም እንደሚገመገም ተናግረዋል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ በቀጣይ ወራት ትኩረት ሰጥቶ የሚያከናውናቸው ስራዎች አቅጣጫዎች እንደሚቀመጥም ዶክተር አብረሃም ገልጸዋል።

በመድረኩ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የቢሮ ኃላፊዎችና የዞን አመራሮች በመሳተፍ ላይ እንደሚገኙ ኢዜአ ዘግቧል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.