Fana: At a Speed of Life!

በአዲስ አበባ የሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን በጋራ ጀመሩ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 26 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ የሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በጋራ ሆነው ችግኝ በመትከል የተቋማቱን የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር አስጀምረዋል።

ተቋማቱ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ እና የኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ ናቸው።

በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመትከል የታቀደውን ስድስት ቢሊየን ችግኝ ለማሳካት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የድርሻቸውን ለመወጣት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ ተገልጿል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ በተለይ ሀገር በቀል እና ለምግብነት የሚውሉ እፅዋትን ለመትከል ማቀዳቸውን የኢቢሲ ዘገባ ያመላክታል ።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.