Fana: At a Speed of Life!

በህንድ በኮቪድ19 በአንድ ቀን 6 ሺህ 148 ሰዎች ለህልፈት ተዳረጉ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 3 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በህንድ በኮቪድ19 በአንድ ቀን ከፍተኛው የሞት መጠን ተመዘገበ፡፡

በሃገሪቱ ባለፉት 24 ሰአታት 6 ሺህ 148 ሰዎች በኮቪድ19 ምክንያት ለህልፈት መዳረጋቸውን የሃገሪቱ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ይህም እስካሁን ከተመዘገቡት ከፍተኛው መሆኑንም አልጀዚራ ሚኒስቴሩን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡

አሁን ላይ በሃገሪቱ ኮቪድ19 ያለባቸው ሰዎች ቁጥር 29 ነጥብ 2 ሚሊየን ሲሆን፥ ባለፉት 24 ሰአታት ብቻ 94 ሺህ 52 ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል፡፡

በቫይረሱ ሳቢያም እስካሁን 359 ሺህ 676 ሰዎች ለህልፈት ተዳርገዋል ነው የተባለው፡፡

ህንድ ከአሜሪካ ቀጥሎ ኮቪድ19 የተያዙ ሰዎች ሲገኙባት በቫይረሱ ሳቢያ ለህልፈት በተዳረጉ ሰዎች ቁጥር ደግሞ ከአሜሪካ እና ብራዚል ቀጥላ ሶስተኛዋ ሃገር ሆናለች፡፡

በሃገሪቱ ላለፉት ሶስት ቀናት በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር መሻሻል ያሳየ ሲሆን፥ ለተከታታይ ቀናትም በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ከ100 ሺህ በታች ሆኗል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.