Fana: At a Speed of Life!

በአጋሮና በጎማ ወረዳ ከ120 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው ፕሮጀክቶች ተመረቁ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 3 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአጋሮ ከተማና በጎማ ወረዳ ከ120 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተመረቁ።

ፕሮጀክቶቹ የመጠጥ ውሃ፣ የውስጥ ለውስጥ መንገድ፣ የሁለተኛ ትውልድ ጤና ኬላዎች፣ የገበያና የወጣቶች መዝናኛ ማዕከላት ናቸው።

ለፕሮጀክቶቹ ግንባታ በአጠቃላይ 123 ሚሊየን ብር ወጪ ሆኗል።

የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አብዱል ሃኪም ሙሉ ፕሮጀክቶቹ ግንባታቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት መዋላቸው ህብረተሰቡ በመንግስት ላይ ያለውን አመኔታ ይጨምራል ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ መንግስት ለህብረተሰቡ ጥያቄ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያልም ነው ያሉት።

በወርቃፈራሁ ያለው

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.