Fana: At a Speed of Life!

የዜጎች ሚና በምርጫ ወቅት በሚል መሪ ቃል በወሎ ዩኒቨርሲቲ ውይይት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ‘‘የዜጎች ሚና በምርጫ ወቅት’’ በሚል መሪ ቃል በወሎ ዩኒቨርሲቲ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በወሎ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት የተዘጋጀ የውይይት መድረክ በዩኒቨርሲቲው ግቢ እየተካሄደ ሲሆን፥ በውይይቱ መግቢያ የኮምቦልቻ ከተማ ከንቲባ ዶክተር ከማል መሀመድ ንግግር አድርገዋል፡፡

በንግግራቸውም ምርጫን መሰረት በማድረግ ሰላምን ሊያደፈርሱ የሚችሉ አካላትን ለመከላከል ከአሁኑ መዘጋጀትና በየአካባቢው ስለ ሰላም መዘመር ያስፈልጋል ብለዋል።

ምርጫን ተገን አድርጎ ከሚመጣ ግጭት ማህበረሰቡን ለመጠበቅም ስለሰላም ግንዛቤ መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተነስቷል።

ከኮምቦልቻ ከደሴና ከደቡብ ወሎ የተመረጡ የህዝብ ተወካዮችና ተፎካካሪ ፓርቲወች የውይይቱ ተሳታፊ ናቸው።

በስንታየሁ መሃመድ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.