Fana: At a Speed of Life!

በደቡብ አፍሪካ ሠላማዊ ሠልፍ ተጠራ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ አፍሪካ ሠላማዊ ሠልፍ መጠራቱን የሠልፉ አስተባባሪ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን ለመደገፍ፣ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ የሚገቡ ኃይሎችን ለመቃወም እና እስካሁን ከኢትዮጵያ ጎን የቆሙ ሀገራትን ለማመስገን ሠላማዊ ሠልፍ መጠራቱን ነው ኮሚቴው ያስታወቀው፡፡

ኮሚቴው በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ከተማ ሰኞ ” ለአፍሪካ ችግር አፍሪካዊ መፍትሄ ” በሚል መሪ ቃል በኢትዮጵያ ላይ በተለያዩ መንገዶች ጫና በማድረግ እና በውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት የሚደረገውን እንቅስቃሴ በመቃወም ሠልፉ ይካሄዳል ብሏል፡፡

በሠልፉ ጣልቃ ገብነትን እንዲያቆሙ ለአሜሪካ እና ለአውሮፖ ህብረት መልዕክት የሚተላለፍ ሲሆን፥ የደቡብ አፍሪካ መንግስትና ህዝብ ደግሞ እስከዛሬ ድረስ ከኢትዮጵያ መንግስት እና ህዝብ ጎን በመቆም ለሰጡት ድጋፍ ምስጋና እንደሚያቀርቡም አስታውቋል፡፡

በደቡብ አፍሪካ የወጣውን የኮቪድ19 መመሪያ ለመጠበቅም በሠልፉ የጥንቃቄ እርምጃዎች እንደሚወሰዱ ኮሚቴው አመላክቷል፡፡

በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ከሃይማኖት ተቋማት ከማህበረሰቡ እና ከመገናኛ ብዙሃን የተውጣጡ የኮሚቴ አባላት ኢትዮጵያውያን በሠልፉ እንዲሳተፉ ጥሪ መቅረቡን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.