Fana: At a Speed of Life!

የመከላከያ ጦር ኮሌጅ እና ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 7 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ መከላከያ የጦር ኮሌጅ እና ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ኢትዮጵያ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ፡፡

ሰነዱን የመከላከያ ጦር ኮሌጅ አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ሀብታሙ ጥላሁን እና የዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በኢትዮጵያ ዋና ተጠሪ ኒኮላስ ቮን አርክ መፈራረማቸውን የኮሌጁ መረጃ ያመላክታል፡፡

ስምምነቱ የዓለም አቀፍ የሠብአዊ መብት ሕግና ተያያዥ የሠብአዊ መብት ድንጋጌዎች ኮሌጁ በሚሰጣቸው ስልጠናዎችና በሚያደርጋቸው ምርምሮች በተሻለ መንገድ እንዲካተቱና በኮሌጁ ሰልጣኞች ከፍ ያለ ግንዛቤ እንዲፈጥሩ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.