Fana: At a Speed of Life!

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ2014 ረቂቀ በጀት ላይ ነገ ይወያያል

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 7 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ በሚያካሂደው መደበኛ ስብሰባው የ2014 ረቂቅ በጀት ላይ በሚቀርብለት የበጀት መግለጫ ላይ ይወያያል።

ምክር ቤቱ በ6ኛ አመት 15ኛ መደበኛ ስብሰባው በረቂቅ አዋጁ ላይ በመወያየት የተለያዩ የውሳኔ ሃሳቦችን መርምሮ ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ የፌደራል መንግስት የ2014 በጀት አመት ረቂቅ በጀት ላይ የበጀት መግለጫ ለምክር ቤቱ የሚያቀርቡ ይሆናል።

ምክር ቤቱ በሚቀርብለት የበጀት መግለጫ ላይ ተወያይቶ ረቂቅ የበጀት አዋጁን ለዝርዝር እይታ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ እንደሚመራም ነው የሚጠበቀው።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.