Fana: At a Speed of Life!

በባህር ዳር እና ጅማ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ ቅስቀሳ መዝጊያ ተካሄደ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 9፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በባህር ዳር እና በጅማ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ ቅስቀሳ መዝጊያ ተካሄደ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጅማ ስታዲየም በመገኘት ለብልፅግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች በመዝጊያ መርሃ ግብሩ ላይ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመልዕክታቸውም ህዝቡን ይዘን ኢትዮጵያን እናሻግራለን ብለዋል፡፡

“አሁን የኢትዮጵያን አንድነት አረጋግጠን ትኩረታችን የአፍሪካን ቀንድ የአፍሪካ ክንድ ማድረግ ነውም” ብለዋል በንግግራቸው።

በባህርዳር ከተማ እየተካሄደ ባለው የብልጽግና ፓርቲ ቅስቀሳ መዝጊያ መርሃ ግብር ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አገኘሁ ተሻገርን ጨምሮ የክልሉ የስራ ሃላፊዎች እንዲሁም የብልጽግና ፓርቲ ደጋፊ የከተማዋ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።

በሙክታር ጠሃ፤ ተጨማሪ መረጃ ከአሚኮ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.