Fana: At a Speed of Life!

በምዕራብ አርሲ ዞን በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ የቆጠራ ውጤቶች ይፋ እየሆኑ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በምዕራብ አርሲ ዞን በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ የቆጠራ ውጤቶች ይፋ እየሆኑ ነው፡፡

የዞኑ የምርጫ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ምክትል አስተባባሪ አቶ ተስፋዬ በቀለ በምርጫ ክልሉ የምርጫ ክልሉ 1 ሚሊየን 101 ሺ 459 መራጮች ድምጻቸውን ሰጥተዋል።

በዞኑ ድምጽ ለመስጠት 1ሚሊየን 143 ሺህ 116 መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን ÷ እስካሁን ባለው መረጃም ከጠቅላላ የዞኑ መራጮች 96 በመቶ ድምጽ ሰጥተዋል።

የዞኑ የምርጫ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ምክትል አስተባባሪ አቶ ተስፋዬ በዞኑ ባሉ 961 የምርጫ ጣቢያዎች ድምፅ መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡

በምስክር ስናፍቅ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.