ትናንት የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ ባልተጠናቀቀባቸው ቦታዎች ላይ ዛሬ ድምጽ እየተሰጠ ነው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ትናንት የድምጽ አሰጣጥ ሂደት ባልተጠናቀቀባቸውቦታዎ በዛሬው ዕለት ድምጽ የመስጠቱ ሂደት ቀጥሎ እየተካሄደ መሆኑን የምርጫ ቦርድ አስታውቋል፡፡
በዚህ መሰረትም በሲዳማ ክልል በሁሉም ምርጫ ክልሎች ከጠዋቱ 5 ሰአት ጀምሮ የድምጽ አሰጣጡ ሂደት የቀጠለ ሲሆን÷ በዛሬው እለትም የሚጠናቀቅ ይሆናል፡፡
በጋምቤላ ክልል ባሉ የተወሰኑ የምርጫ ክልሎች ተቋርጦ የነበረው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ዛሬ ከቀኑ 8 ሰአት ጀምሮ የሚቀጥል ሲሆን በዛሬው እለት ይጠናቀቃልም ነው የተባለው።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በሁለት ምርጫ ክልሎች ያለው ድምጽ አሰጣጥ ሂደት ለጊዜው የቆመ ሲሆን÷ ቁሳቁሶች በሙሉ ታሽገው እንዲጠበቁ ቦርዱ ለአስፈጻሚዎች አሳውቋል።
ቦርዱ የሚቀጥለው የድምፅ አሰጣጥ ሁኔታ እና እስካሁን ያለውን ሂደት ገምግሞ የደረሰበትን ውሳኔ እንደሚያሳውቀም ጠቁሟል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!