Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞች የላሙ ወደብን ሊጎበኙ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 17 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)ከተለያዩ የግልና የመንግስት መገናኛ ብዙሃን የተውጣጡ ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞች የላሙ ወደብን ሊጎበኙ ነው።

በቅርቡ በኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የተመረቀው የላሙ ወደብ በኢትዮጵያ፣ ኬንያና ደቡብ ሱዳን የተጀመረ የጋራ ፕሮጀክት ነው፡፡

ጋዜጠኞቹ  ከሰኔ 17 እስከ 20 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ በኬንያ በሚኖራቸው ቆይታ ከላሙ ወደብ  በተጨማሪ ተዛማጅ ፕሮጀክቶችን ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ከዚያም ባለፈ ኢትዮጵያውያን የዳያስፖራ አባላት በአገራቸው የሚያደርጉትን ተሣትፎ የተመለከተ  ጉብኝት እንደሚያደርጉ ኬንያ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.