Fana: At a Speed of Life!

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የኢንዱስትሪ ትስስር ፖሊሲ የህግ ማዕቀፎች ማረጋገጫ አውደ ጥናት ተካሄደ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 19 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ምርምር ተቋማትና የኢንዱስትሪ ትስስር ፖሊሲ የህግ ማዕቀፎች ማረጋገጫ አውደጥናት በቢሾፍቱ ከተማ ተካሄደ።

ዩኒቨርሲቲዎች፣ የምርምር ተቋማት፣ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት፣ መንግስትና ኢንዱስትሪዎችን የሚያስተሳስር የህግ ማዕቀፍ ግብአት የሚሆኑ ምክረ ሃሳቦችም ተነስተውበታል።

የኢትዮጵያን ምርትና ምርታማነት ለማሣደግ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ስራዎች ባለቤት የሆኑ አካላት በጋራ አለመስራታቸው ዋናው ችግር መሆኑ ተገልጿል፡፡

ከዚህ አንጻርም ችግሮቹን ለመፍታት በጋራ መስራት ይገባል ብለዋል።

የኢንዱስትሪ ትስስር መፈጠሩ ብቁ ለውድድር የሚቀርብና በተግባር አቅሙን ያጎለበተ የሠው ሀይል ለማፍራትና የስራ አጥነት ችግርም ለመቅረፍ ይረዳል ተብሏል።

በሰላማዊት ተስፋዬ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.