Fana: At a Speed of Life!

የኤሌክትሪክ መቆራረጥ የውሃ ስርጭት ላይ ጫና እያሳደረ ነው – የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 19 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ሰሞኑን በተፈጠረው የኤሌክትሪክ መቆራረጥ የውሃ ምርት እና ስርጭት ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ መሆኑን የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

ባለስልጣኑ የኤሌትሪክ መቆራረጥ ችግሩ በአቃቂ ጉድጓዶች እና ግፊት መስጫ ጣቢያዎች ላይ መፈጠሩን ገልጹ፥ ይህም ውሃ ለደንበኞቹ በወጣው መረሀ ግብር መሰረት እንዳይሰጥ ችግር እንደፈጠረበት አስታውቋል፡፡

በዚህም ገላን አካባቢ፣ ሳሪስ፣ ሀና ማርያም፣ ሀይሌ ጋርመንት፣ ላፍቶ፣ ጀሞ፣ ቆሬ፣ ሳር ቤት፣ ሜክሲኮ፣ ልደታ፣ ጌጃ ሰፈር እና ቤቴል አካባቢዎች ውሃ ለማሰራጨት አልተቻለም ነው ያለው፡፡

ከዚህ ባለፈም በለገዳዲ ጉድጓዶች ላይ በየሰዓቱ የሚከሰተው የኤሌክትሪክ መቆራረጥ በባለስልጣኑ አገልግሎት ላይ ጫና እያሳደረ መሆኑን የባለስልጣኑ መረጃ ያመላክታል፡፡

ከዚህ አንጻርም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የችግሩን ስፋት በመረዳት አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጠውም ጠይቋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.