Fana: At a Speed of Life!

በኬንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሄደ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 19 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኬንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጅ ኬንያውያን የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሄደ።

የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ የኬንያ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣናት የተገኙ ሲሆን ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ ቀጠናውን ለማስተሳሰር እያደረገች ያለውን ጥረት አድንቀዋል።

1 ሚሊየን ችግኞችን በዘንድሮው ክረምት በኬንያ የሚተከል ሲሆን እንዲህ አይነት መርሃ ግብሮች የሁለቱን ሀገራት ዲፕሎማሲ በማጠናከሩ ረገድ ሚናው ትልቅ እንደሚሆን ተጠቁሟል።

ኬንያ ዛፍ የመንከባከብ እና አካባቢ ጥበቃ ላይ ማህበረሰቡ ላይ የሰራችው ስራን ኢትዮጵያ ልትጋራው የሚገባ መሆኑ ተነግሯል።

በብስራት መለሰ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.