Fana: At a Speed of Life!

የጀነራል ሰዓረ መኮንንና የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ መታሰቢያ ሃውልት በቅርቡ ይመረቃል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀድሞው የኢፌዴሪ ጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀነራል ሰዓረ መኮንንና የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ መታሰቢያ ሃውልት ስራ መጠናቀቁን ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል፡፡

ከተማ አስተዳደሩ “ወታደር ብሄር የለውም” በሚል ንግግራቸው የሚታወቁት የጀነራል ሰዓረ መኮንን እና የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ መታሰቢያ ሃውልት ስራ ማጠናቀቁን ወይዘሮ አዳነች በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል፡፡

ሃውልቱ በቅርቡ ወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች እና አድናቂዎቻቸው በተገኙበት እንደሚመረቅም ምክትል ከንቲባዋ ጠቁመዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.