አምባሳደር ጀማል በክር ከባህሬን የዲፕሎማሲ ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ
በተያያዘም አምባሳደሩ ከባህሬን ምክትል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር አቡዱላህ ፋይሰል አል ዶሰሪ ጋር በሁለትዮሽ፣ ቀጠናዊና ክልላዊ ጉዳዮች ዙሪያ በበይነ-መረብ ተወያይተዋል፡፡
በዚህ ወቅት አምባሳደር ጀማል የሁለቱን ሃገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ከዚህ ቀደም የተደረሱ የሰው ሃይል ስምሪት፣ የፖለቲካ ምክክርና ቪዛ ስምምነቶች ወደ ትግበራ እንዲገቡ ለማድረግ እየተሰሩ ያሉ ጉዳዮችን አንስተዋል፡፡
በዚህ ወቅት አምባሳደሩ 6ኛውን ሃገራዊ ምርጫ በተመለከተ፣ የትግራይ ክልል መልሶ ግንባታና መቋቋም፣ የሰብዓዊ ፍላጎቶች ለማሟላላት እንዲሁም የሰብዓዊ ጥሰት ለማጣራት እየተደረጉ ያሉ ተቋማዊ እንቅቃሴዎችን በተመለከተ እንዲሁም የህዳሴ ግድብን እና የኢትዮ-ሱዳን የድንበር አለመግባባትን በተመለከተ ገለጻ አድርገዋል፡፡