Fana: At a Speed of Life!

ክህደት የፈጸሙ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በጽኑ እስራት ተቀጡ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በሀገርና በሀገሪቱ ሰራዊት ላይ ክህደት በመፈፀም ከፍተኛ ጉዳት ያደረሱ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እስከ 18 ዓመት የሚደርስ የፅኑ እስራት ቅጣት ተላለፈባቸው።

የደቡብ ዕዝ ቀዳማዊ የጦር ፍርድ ቤት ባስቻለው ወታደራዊ ፍርድ ቤት አስር ተከሳሾች ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው በሰሩት ወንጀል መጠን የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ከሀገር አፍራሽ አሸባሪዎች ጋር ሚስጥራዊ ግንኙነት በመፍጠር የሀገር ደህንነት አደጋ ላይ በመጣል፣ ክህደት በመፈፀም አሸባሪዎቹን የህወሓት ጁንታ ለመቀላቀል ማሴር፣ ለሸኔ መረጃ ማቀበል፣ ከግዳጅ ቀጠና በመሸሽ የወገን ጦርን ለአደጋ ማጋለጥ፣ ያለ በቂ ምክንያት ሲቪሎችን መግደል፣ የበላይን ትዕዛዝ ችላ በማለት ለንፁሐን ሞት ምክንያት መሆንና የመንግሥትና የህዝብን ወታደራዊ ንብረትን ይዞ ለመሸሽ ሙከራ ማድረግ የሚሉ ክሶች ዋነኛ ጭብጥ ሆኖ ቀርቧል፡፡

ወታደራዊ ፍርድ ቤቱ ግራ ቀኙን ሲመረምር ቆይቶ ተከሳሾች እራሳቸውን መከላከል ባለመቻላው የቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

በዚህ መሰረት፡-

1. ሻለቃ ክፍሌ ካሳይ በ17 አመት ፅኑ እስራት፣
2. ኮሎኔል ክፍሌ ፍሰሃዬ በ14 ከ 2 ወር ፅኑ እስራት፣
3. ሀምሳ አለቃ መብራቱ ጥላዬ በ18 አመት ፅኑ እስራት፣
4. መሰረታዊ ወታደር መኮንን ክንፈ በ13 አመት ፅኑ እስራት፣
5. ሀምሳ አለቃ ፈረደ ይባስ በ11 አመት እስራት፣
6. ምክትል አስር አለቃ ሀጎስ በርሄ በ11 አመት ፅኑ እስራት፣
7. ምክትል ክፍሌ ንጉስ በ9 አመት ፅኑ እስራት፣
8. ኮሎኔል ካሱ ሀብቱ በ11 አመት ከ2 ወር፣
9. ኮሎኔል ሀጎስ አሰፋ በ8 አመት ፅኑ እስራት እና
10. ሌተናል ኮሎኔል ሀይላይ ገብሩ በ10 አመት ከ2 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ወታደራዊ ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቷል፡፡

በቀጣይም ከ150 በሚበልጡ ተጠርጣሪዎች ላይ የፍርድ ሂደት እንደሚታይ ተገልጿል፡፡

በቢቂላ ቱፋ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.