ባለስልጣኑ ከ1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ሰበሰበ
አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 24 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን በተጠናቀቀው በጀት አመት ከ1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡
ገቢው በዋናነት ከውሃ ሽያጭና ከሌሎች የአገልግሎት ዘርፎች የተሰበሰበ ነው ብሏል፡፡
ባለስልጣኑ በበጀት ዓመቱ ከ1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ለመሰብሰብ አቅዶ 1 ቢሊየን 389 ሚሊየን 19 ብር በመሰብሰብ የእቅዱን 85 በመቶ ማሳካቱን ከአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ተጠቃሚዎች በወቅቱ የአገልግሎት ክፍያቸውን ያለመፈጸም የታየ ችግር ሲሆን÷ ባለስልጣኑ በበጀት አመቱ ለረጅም ጊዜ ውዝፋቸውን ያልከፈሉ ከ52 ሺህ በላይ ደንበኞች የውሃ አገልግሎት በማቋረጥ ከቅጣት ጋር ለመሰብሰብ መገደዱን ገልጿል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!