Fana: At a Speed of Life!

የደቡብ ወሎ ዞን የወጣቶች የክተት ዘመቻ መድረክ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ወሎ ዞን የወጣቶች የክተት ዘመቻ መድረክ በመቅደላ አምባ ዮኒቨርሲቲ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በመድረኩ የአማራ ክልል የዞን እና የመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን÷ የክተት አዋጁን ተቀብለው የተቀላቀሉ ከ1 ሺህ 500 በላይ የሚሆኑ ወጣቶችም ተሳታፊ ናቸው።

በውይይት መድረኩ ወጣቶች የሀገራቸውን ህልውና የመጠበቅ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ መልዕክት ተላልፏል።

በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ አስተባባሪ ዶክተር አለሙ ስሜ እንዲሁም የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተተዳዳሪ አቶ ሰይድ መሀመድ ተገኝተዋል።

በሀብታሙ ተ/ስላሴ፣ በከድር መሀመድና በመሀመድ አሊ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.