Fana: At a Speed of Life!

በከተማ ግብርና አበረታች ውጤቶች መመዝገብ ጀምረዋል – ወ/ሮ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 26፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በከተማ ግብርና ዘርፉ የሚገኘው ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ በመሆኑ አበረታች ውጤቶች መመዝገብ መጀመሩን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ገለፁ፡፡

ምክትል ከንቲባዋ በፌስቡክ ገፃቸው ባሰሰሩት ፅሁፍ÷ “ከተማችን የከተማ ግብርና ልምድ እንዲዳብር፣ ከዘርፉ የሚገኘው ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር በርካታ ስራዎችን እያከናወንን ስለሆነ አበረታች ውጤቶች ማስመዝገብ ጀምረናል” ብለዋል።

በጓሮ አትክልት ልማት፣ በወተትና የወተት ተዋፅዖ፣ በዶሮና እንቁላል ልማት፣ በሰብል ምርት ላይ በጎ ጅምር መታየቱ በቀጣይ እንደ ከተማ ይበልጥ ውጤታማ መሆን እንደምንችል ማማሳያ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

በምግብ ራስን መቻልም የክብራችን ማስጠበቂያ አንዱ መንገድ ነው ሲሉም ጠቅሰዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.