Fana: At a Speed of Life!

በህወሓት በሬ ወለደ ወሬ የሚፈታ ህዝብ የለንም – አቶ ከበደ ካሣ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በህወሓት በሬ ወለደ ወሬ የሚፈታ ህዝብ የለንም ሲሉ የሀይቅ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ገለጹ፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ እንዳሉት÷ አሸባሪው ህወሓት እየተጠቀመበት ያለው የውሸት ፕሮፓጋንዳ ጊዜው ያለፈበት ስልት ነው ብለዋል።

የከተማችን ወጣትና ነዋሪዎች የሽብር ቡድኑን እኩይ ተግባር በሚገባ ስለሚያውቅ በወሬ አይፈታም ፤ ደቡብ ወሎ ምድርን ሳይነካም ቀብሩን እንፈጽማለን ነው ያሉት።

የህወሓት ተላላኪወችን ወሬ የሚያናፍሱ ግለሰቦች የጁንታ ቡድኑ ተከፋዮች በመሆናቸው ማህበረሰቡ በያሉበት ለጸጥታ ሀይሉ እንዲጠቁምና ይዞም እንዲያስረክብ ጥሪ አቅርበዋል።

የከተማው ወጣቶች ተደራጅተው ወንበዴውን ከመከላከያ ሠራዊት ጋር በመሆን ባለበት እየቀበሩት መሆኑንም ጠቁመዋል።

የከተማው ህዝብ ሰርጎ ገቦችን እየለየ አካባቢውን እንዲጠብቅም አሳስበዋል።

በአለባቸው አባተ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.