Fana: At a Speed of Life!

የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን አስመርቀዋል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 29፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ያስተማሯቸውን ተማሪዎች ማስመረቃቸውን ከዩኒቨርሲቲዎቻቸው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ ያስተማራቸዉን 3ሺህ 237 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡

የሠመራ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎችና መርሃግብሮች ያስተማራቸውን 246 ተመራቂዎችን ያስመረቀ ሲሆን÷ ከተመራቂዎች መካከልም 69ኙ ሴት ተማሪዎች ናቸው፡፡

በተመሳሳይ ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በቴፒ ግቢ ለ13ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን 1ሺህ 38 ተማሪዎችን አስመርቋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.