Fana: At a Speed of Life!

የድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ጥሩ ለፈጸሙ ሠራተኞቹ ዕውቅና ሰጠ

 

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ውስጥ መልካም አፈፃፀም ላሳዩ ሠራተኞቹ ዕውቅና ሰጠ።

የሣይስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከዩኒቨርሲቲው ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የአስተዳደር ቢዝነስና የአይሲቲ ፎረም ዛሬ ተጠናቋል።

የ2013 ትምህርት ዘመን በኮቪድና በተለያዩ የፀጥታ መደፍረሶች የታጀበ እንደነበር የገለፁት የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ዑባህ አደም፣ በእነዚህ መሠናከሎች ላልተበገሩት የዩኒቨርስቲው መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በተለይም በኮቪድ 19 ባክኖ የነበረውን የ2012 ትምህርት ዘመን ለማካካስ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት፣ ተደራራቢ ኮርሶችን ሲሰጡ የነበሩ መምህራን ከስራ ሃላፊነታቸውም በላይ የዜግነት ግዴታቸውን ተወጥተዋል ብለዋል።

በመድረኩ በተመራቂ የአርክቴክቸር ተማሪዎች የተሠራ የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ዑባህ አደም ፎቶ ለጨረታ ቀርቦ በ22 ሺ ብር ተሸጧል። ከጨረታው የተገኘው ገንዘብም ለበጎ አድራጎት ስራ እንደሚውል ተገልጿል።

በእዮናዳብ አንዱዓለም

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.