የኢትዮጵያ ቮሊቦል ብሔራዊ ቡድን የደቡብ ሱዳን አቻውን 3 ለ 2 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ የወንዶች ቮሊቦል ሻምፒዮና ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቮሊቦል ብሔራዊ ቡድን ደቡብ ሱዳን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል ።
ከነሀሴ 30 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በሩዋንዳ ኪጋሊ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው የአፍሪካ የወንዶች ቮሊቦል ሻምፒዮና እስከ መስከረም 6 ቀን 2014 ዓ.ም የሚቀጥል መሆኑ ተመላክቷል።
በሻምፒዮናው ኢትዮጵያን ጨምሮ 16 ሀገራት አእየተሳተፉ የሚገኙ ሲሆን፥ውድድሩም በ4 ምድብ ተከፍሎ ይካሄዳል።
የኢትዮጵያ ቮሊቦል ብሔራዊ ቡድን በምድብ 2 ከቱኒዚያ ፣ ናይጀሪያ እና ደቡብ ሱዳን ጋር ተደልድሏል።
በዚህም የኢትዮጵያ ቮሊቦል ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ከደቡብ ሱዳን ጋር ባደረገው ጨዋታ 3 ለ 2 ማሸነፉን ከስፖርት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
![](https://scontent.fadd1-1.fna.fbcdn.net/v/t1.6435-9/s600x600/241304728_4369830879774284_211342938282413745_n.jpg?_nc_cat=107&ccb=1-5&_nc_sid=730e14&_nc_ohc=ItRbVtE1PwgAX8bDjAv&_nc_ht=scontent.fadd1-1.fna&oh=33db408561c6af691a103497ce558b03&oe=615EB238)
![](https://scontent.fadd1-1.fna.fbcdn.net/v/t1.6435-9/p600x600/241359134_4369831146440924_478006212933319464_n.jpg?_nc_cat=103&ccb=1-5&_nc_sid=730e14&_nc_ohc=YMQFKEa6L1gAX8cc6WY&_nc_ht=scontent.fadd1-1.fna&oh=a6bf16a2dda514645026dcd7511362bb&oe=615D7C61)
![](https://scontent.fadd1-1.fna.fbcdn.net/v/t1.6435-9/s600x600/241529982_4369831586440880_8413268997378357742_n.jpg?_nc_cat=100&ccb=1-5&_nc_sid=730e14&_nc_ohc=E4M3makNzmgAX9UFsDi&_nc_ht=scontent.fadd1-1.fna&oh=3456f2c875c73ffb9922ae54f28873b6&oe=615CAB06)
0
People Reached
395
Engagements
Boost Post
375
6 Comments
14 Shares
Like
Comment
Share